Skip to main content

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የዳኝነት አስተዳደር ዋና ጉባኤ ሰኔ 19/2017 በሀላባ ከተማ ባካሄደው 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል ።

በዚሁ መሰረት

1 , የዳኞች ሹመት ምልመላና መረጣን በማጠናቀቅ ለክልሉ ምክር ቤት የሚቀርብ ለከፍተኛ ፍ/ቤት ወንድ 8 ሴት 2 በድምሩ 10

ለወረዳና ለከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ወንድ 34 ሴት 1 በድምሩ 35 እጩ ዳኞችን ለማቅረብ አጽድቋል።

2, በቀረበው 9 የዲሲፒሊን መዝገቦች በ3 መዝገቦች ላይ በንዑስ ጉባኤ የተወሰነውን የቅጣት ውሳኔ በማሻሻል ወስኗል፡፡

በ 3 መዝገቦች የዲሲፕሊን ክስ የቀረበባቸው ዳኞች ላይ ተጨማሪ ማጣራት በማድረግ ለቀጣይ ጉባኤ እንዲቀርብ ወስኗል፡፡

በ3. የዲሲፒሊን መዝገቦች ላይ ክስ የቀረበባቸው ዳኞች የንዑስ ጉባኤው የሰጠው የውሳኔ ሃሳብ አግባብ ነው በማለት ወስኗል፡፡

3, የዳኞችና ባለሞያዎች 6 የዝውውር ጥያቄን ተቀብሎ አጽድቋል። በመጨረሻም የ 3 

ረ/ዳኞች የስራ መልቀቂያ በመቀበል በገዛ ፍቃዳቸው ክስራ እንዲሰናበቱ ውሳኔውን አስተላልፏል።

Image
dagninet