Skip to main content

 

አቶ ሰለሞን መሽሻ 

የመንግስት ኮሙኒኬሽን እና ሚድያ ግንኙነት ዳሬክቶሬት

 

 

 

 

 

 

 

የጠቅላይ ፍ/ቤት የህዝብ ግንኙነት መሠረታዊ ዓላማዎች

  1. የጠቅላይ ፍ/ቤቱ የሚመራባቸዉን ህጎች የሚያስፈፅማቸዉን ደንቦችና መመሪያዎች የሚተልማቸዉ የልማት ዐቅዶችና አፈፃፀማቸዉን በየጊዜዉ ለህዘቡ ለተገልጋዩ በልዩ ልዩ መንገድ ማስተዋወቅ፡፡
  2. ጠቅላይ ፍ/ቤቱ በሚሠጣቸዉ አገለረገረሎቶች ላይ የሚሰነዘሩ አስተያየቶችን ተከትሎ በማጥናትና በመገምገም በመልካም ጎን የቀረቡ ከሆነ ማሻሻያ የሚያገኝበትን መንገድ መጠቆም፡ ለአሉታዊና በአፍራሽነት ለቀረቡት  ደግሞ የማስተባበያ ሀሳብ መስጠት
  3. የጠቅላይ ፍ/ቤት የበላይ ሀላፊዎችና ሌሎች የስራ ዘርፎች በኢንፎረሜሽን ኮሚኒኬሽን ዘርፍና በሚድያ አጠቃቀም ዙሪያ የማማከር አገልግሎት መስጠት፡፡
  4. ጠ/ፍ/ቤትን የሚመለከቱ ማንኛዉም አይነት መረጃዎችና ጥያቄ ስቀርቡለት ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ የስራ ክፍሎች መረጃዎችን አሰባስቦ በማጠናቀር ጠያቄዉን ላቀረቡት አካላት እንድደርሳቸዉ ማድረግ፡፡
  5. በአመራርና በሠራተኛዉ በሰራተኛዉ መካከል እንዲሁም በመላ ሰራተኛም ጤናማ የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲሰፍን  የመ/ቤቱን ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት የጋራ ዓላማና ተግባር እንዲኖራቸዉ የማድረግ እንዲሁም በስራዉና በመ/ቤቱ ላይ የባለቤትነት ስሜት አሳድረዉ እርስ በርስ የሚተጋገዙበትና የሚተባበሩበት  ሁኔታ ማመቻቸት፡፡
  6. ከሌሎች መ/ቤቶች ፡ተቋማት ፡ድርግቶችና ግለሰቦች ጋር የሚኖረዉ የሁለትዩሽ ግንኙነት እንዲሰምር የተመቻቸ ሁኔታ መፍጠር በዉስጥ ያሉ  ፕሮግራሞች ና ተቋማዊ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ እንዲታወቅና እነዲሰርፁ በማድረግ በአንድ በኩል የዜጎችን ግንዛቤ አሳድጎ ንቁ ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ሊያስችል በሌላ በኩል ደግሞ የተቋሙን ምላሽ የመስጠት ብቃት ያረጋግጣል፡፡